07/04/2022
ኢትዮጵያ በሃይማኖትም ሆነ በፖለቲካው ሴኩላሪዝምን ተግብራ አታውቅም!
©Musa Adem oumer
የማንነት ፖለቲካ እንደ ሽንኩርት ነው አንዱን ቅርፊት በገፈፈከው ቁጥር ሌላው ወጥቶ ይጠብቀሃል። በቅንነት እና በእውነተኛ ፍትህ ካልሆነ በስተቀር በማጭበርበር፤ በማስመሰል እና ፖሊሲዎችን ተገን በማድረግ ለማስተዳደር መሞከር የጉዳዩን ክብደት ካለመገንዘብ ወይ ደግሞ በማን አለብኝነት የሚታለፍ አይደለም መዘዙ ብዙ ነውና።
ሴኩላሪዝም ሃይማኖትን ተው ማለት አይደለም!
አንብቦ መረዳት እንደሚቻለው ሴኩላሪዝም ሃይማኖቶች በትምህርትና ሌሎች ማህበራዊ ጉዳዮች የፖሊሲና የአፈፃፀም ሂደቶችን Influence ማድረግ የለባቸውም ማለት እንጂ ሃይማኖት አልባ ማህበረሰብ መፍጠር ማለት አይደለም።
ሀገራችን ለሌሎች ክብር በሰጠህ ቁጥር ክብር የምታጣበት ሀገር መሆን የለባትም ተከባብረን ለሁላችንም የምትሆን ሀገር ነው መገንባት ያለብን።
እስቲ የተወሰኑ የሃይማኖት ጥያቄዎችን ላንሳ
1/የሁላችንም ቀዳማዊት እመቤት ከአራት ኪሎ ቤተመንግስት የመዝሙር ነጠላ ዜማ አልጋበዙንም?
2/የሀገሪቱ ጠቅላይ ሚኒስትር የሁሉንም ሃይማኖቶች ቃላቶች አብዩዝ በሚያደርግ ልክ በፓስተር ቶን ፖለቲካን አልጋቱንም?
3/ በሁሉም የመንግሥት መስሪያ ቤቶች ማለት በሚቻል መልኩ የመንግስት ሠራተኞች በተለይ ፀሃፊዎች ወይ ቅድስ ማሪያም ወይ ደግሞ የኢየሱስን ፎቶ በትልቁ ለጥፈው አልተቀመጡምን?
4/ከዚህም እጅግ በባሰ መልኩ በመስሪያ ቤት ረደጃ የሚካኤልን ፀበል ፃድቅ ተዘጋጅቶ ቢሮ አይዘጋምን?
5/ከዚህ እጅግ በተቃረነ መልኩ ማንም እርኩስ የሚጨፍርበት በአብዮት አደባባይ ህዝበ ሙስሊሙ ፆሙን ውሎ ስለ ሀገሩ እየፀለየ ለሰላሳ ደቂቃ ተሰብስቤ ላፍጥር ስል ውሻ አልተደረገም?
6/ኢትዮጵያዊነቱን ለነዛ የዜግነት መዳቢዎች ለማረጋገጥ "ግድቡ የኔነው" በማለት በሚልዮኖች ብር አላዋጣምን?
7/በሁሉም ትምህርት ቤቶች አብይ ፆም ገብቷል ተብሎ የሁሉም የተማሪውች ምግብ ወደ የፆም ምግብ አልተቀየረምን?
8/አሁን ረመዳን ስለገባ ሁሉም ተማሪዎች መመገቡን አቁሟልን?
9/አስተዳዳሪው ፓርቲ የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ኃላፊዎች ሳይቀር በማዕከላዊ ኮሚቴ አባልነት አልያዘምን?
10/መንግስት ብቸኛውን የሙስሊሞች ተቋም በሆነው የመጅስሊስ እና የሸሪዓ ፍርድ ቤቶች ውስጥ ግልፅ በሆነ ሁኔታ ጣልቃ አልገባምን?
11/ ይህ ሁሉ ሃይማኖታዊ ትርዒቶች በሚፈፀምበት ሀገር ላይ ስለ ሴኩላሪዝም ማውራት እንዴትስ ይቻለናል?
አላበዛባችሁም ብዬ እንጂ ሺህ ጉዳዮችን መዘርዘር ይቻላል አለመናገር ደግሞ አለማወቃችንን አያመለክትም። ተማሪዎች ሶሏታቸውን ይስገዱ፣ ፆማቸውን ይፁሙ፤ ሂጃባቸውንም ይልበሱ፣ ትምህታቸውን ይማሩ ይህ ማንንም አይጎዳም። አትሰግዱም እያልን ይሀው መዓት ከሰማይ እየወረደብን ነውና እንንቃ!