12/07/2026
የታሰረ የመንግሥት ሠራተኛ የደሞዝ መብት በአዲሱ አዋጅ (1334/2016)
አንድ ሠራተኛ በወንጀል ተጠርጥሮ በቁጥጥር ሥር ቢውል ወይም በጊዜ ቀጠሮ ቢታሰር የሚከተሉት ሕጋዊ መብቶች አሉት፦
1️⃣ የግማሽ ደሞዝ ክፍያ (50%)
ሠራተኛው በቁጥጥር ሥር በዋለበት ከመጀመሪያው ቀን ጀምሮ ለ 3 ወራት ድረስ የመሠረታዊ ደሞዙን 50% የማግኘት መብት አለው።
ተቋሙ "ሥራ አልገባህም" በሚል ምክንያት ደሞዝ ሙሉ በሙሉ ሊያቆም አይችልም።
2️⃣ የጊዜ ገደብ (3 ወራት)
እስሩ ከ 3 ወራት በላይ የሚቆይ ከሆነ ግን፣ ከሦስተኛው ወር በኋላ ያለው ክፍያ ይታገዳል።
ነገር ግን ሠራተኛው በነፃ ከተለቀቀ የታገደው ደሞዝ በሙሉ ይታሰባል።
3️⃣ በነፃ ሲለቀቅ የሚከፈል ካሳ
ሠራተኛው በነፃ ከተለቀቀ ወይም ክሱ ከተቋረጠ፦
ሳይከፈለው የቀረው 50% ደሞዝ በአንድ ጊዜ ተሰልቶ ይከፈለዋል።
በእስር የቆየበት ጊዜ እንደ ሥራ ዘመን ይቆጠርለታል።
ወደ ቀድሞ ሥራው የመመለስ ሙሉ መብት አለው።
4️⃣ ደሞዝ ሙሉ በሙሉ የሚቆመው መቼ ነው?
ሠራተኛው በፍርድ ቤት ጥፋተኛ ተብሎ የእስራት ፍርድ ሲበየንበት ብቻ ተቋሙ የሥራ ውሉን አቋርጦ ደሞዝ ሊያቆም ይችላል።
መንግሥት መሥሪያ ቤቱ በአዲሱ አዋጅ መሠረት ሠራተኛው እስካልተፈረደበት ድረስ ደሞዝ አልከፍልም ማለት አይችልም! ግማሽ ደሞዙን የመክፈል ግዴታ አለበት