GetIt Addis

GetIt Addis Shop smarter, not harder. Find it all at GetIt Addis.

14/03/2024

Shiferaw

ከልብ የመነጨ ይቅርታን እጠይቃለሁ።
በትግራይ ጦርነት ወቅት ከወ*ያኔ እንቅስቃሴና ግብ አንፃር ይዤ
የነበረው አቋም ትክክለኛ እንደነበር አልጠራጠርም። ለጦርነቱ ወ*ያኔ የነበረውን ወሳኝ ሚናም በማለባበስ ተጠያቂነቱን ከወ*ያኔ ላይ ለማውረድ የሚደረገው ጥረትም ነጭ ውሸት ስለሆን አልቀበለውም።
ከዚህ አንፃር በጦርነቱ ወቅት ይዤ የነበረው አቋምና የአቅሜን ያህል ያደረግሁትም ድጋፍ ተገቢ ነበር ብዬ አምናለሁ።
በሌላ በኩል ደግሞ ትልቅ ፣ በጣም ትልቅ ስህተት መሳሳቴን ተረድቻለሁ ፤ በዚህም ልቤ በፀፀት አለንጋ ይገረፋል።
ይኸውም ፥ ጦርነቱ ከተጀመረ ጥቂት ሳምንታት አንስቶ በትግራይ ንፀሃን ላይ እየደረሰ ነው ይባሉ የነበሩ የጅምላ ግድያ፣ አስገድዶ መድፈር፣ የምግብ አቅርቦት እገታ፣ የዘፈቀደ እስርና እንግልት ወዘተ ሁሉ በወ*ያኔ እና በፕሮፓጋንዳ ሰራዊቱ የሚነዛ የሀሰት ክስ ይመስለኝ ነበር። ይህ እንዲመስለኝ ደግሞ ከወ*ያኔ ተመሳሳይ ባህሪ አንስቶ በርካታ ሌሎች አሳሳች ምክንያቶችም ሚና ነበራቸው። በርግጥ በወ*ያኔ የእስስትነትና ጨካኝነት ሆን ተብለው የተፈጠሩ ሴራዎች እንደነበሩም እውነት ነው። ይሁንና ከዚህ ባሻገር በርግጥም ንፁሃን በተጠቀሱት መልኩ የበርካታ ግፎች ሰለባ እንደነበሩ ከተረዳሁ ወራት ተቆጥረዋል። በዚህም የተነሳ ፥ በንፁሃን ላይ ይደርስ የነበረን ግፍ እውነትነቱን ለማረጋገጥ በቂ ጥረት ሳላደርግ በመቅረቴ ጆሮ ዳባ ልበስ ላልኩት በደል፣ ተፈፅመው ሳለ እንዳልተፈፀሙ እርግጠኛ ሆኜ የማይገባ ሚና በመጫወቴ ልቤ እጅግ፣ እጅግ ያዝናል።
ከክፉ መንፈስ ባልነሳም ፥ ለዚህ ያልተገባ ሚናዬና የንፁሃንን ህመም ያልተጋራሁ በመሆኔ እጅግ ከባድ ስህተት ሰርቼ ነበርና በዚህ በጣም አዝናለሁ ፤ በፀፀት ከተሞላ ልብ በመነጨም ለዚህ ተግባሬ ይቅርታን እጠይቃለሁ።

ስንት ሪፖርት አካውንታችንን ሚዘጋ ይመስላቹሃል ? ሀክ ሲደረግስ እንዴት ነው ሚያረጉብን ምናስመልሰውስ ? ኮመንት አርገን ስድብ ነው ስንባልስ ኧረ በህግ አንልም። በአጠቃላይ እነዚህ የፌስቡክ...
14/03/2024

ስንት ሪፖርት አካውንታችንን ሚዘጋ ይመስላቹሃል ? ሀክ ሲደረግስ እንዴት ነው ሚያረጉብን ምናስመልሰውስ ? ኮመንት አርገን ስድብ ነው ስንባልስ ኧረ በህግ አንልም። በአጠቃላይ እነዚህ የፌስቡክ ተግዳሮቶች ናቸው።

1. የፌስቡክ ጠለፋ :Facebook Hacking
አብዛኛው ኢትዮጲያዊ የጠለፋ (hacking) ትርጉም የተረዳ አይመስለኝም። ብዙዎች ከCracking ጋር ሲያምታቱ ይስተዋላል። አንድ ሰው ፓስዎርዳችንን አውቆ ወደአካውንታችን ሲገባ Hacking ሲባል ይለፍ ቃል (password) ሳያቅ ነገር ግን በሆነ መንገድ መቀየር አልያም መስበር ሲችል ደግሞ Cracking ይሰኛል። ጠለፋ (hacking) ሲካሄድብን እንዴት እንወቅ?
አንድ አካውንታችንን የጠለፈ ግለሰብ እኛ እንደምናስበው ስድብ የሚፖስት ፣ አሊያም አካውንታችንን ዘግቶ የሚያስቀር ብሎም እኛም እሱም አካውንቱን የምንጠቀምበትን መድረክ የሚፈጥር አይደለም። የጠለፈን ግለሰብ በአካውንታችን ብዙ ነገር የሚለጥፍ ሲሆን እኛም ከሱ ለመቀማት የምናካሂደው ሙከራ በቀላሉ እና በሰአታት ዝም ብሎ መነካካት የሚቀየር አይደለም።
ፌስቡካችን በተለያየ መንገድ የመጠለፍ አደጋ ውስጥ ሊገባ ይችላል።
ሀ) ሰዎች የሚልኩትን ሊንኮች ሁሉ በመነካካት ከፍቶ ለመግባት በመሞከር
ለ) በሰዎች ማስታወቂያ አሊያም እምነት በመጣል በቴሌግራም መሰል ሌሎች ገፆች ላይ የሚለቀቁ አፕሊኬሽኖችን ስልክ ላይ በመጫን
ሐ) ፓስወርዳችን በሰው ፊት በመሙላት እንዲሁም ቀላል ስለሆነ
መ) በተሳሳተ መረጃ ፓስወርዳችንን በመስጠት (Social Engineering)
እንዴት እንከላከል?
ሀ) የፌስቡክ ፓስወርዳችንን የኮምፒዩተር ሲስተም ከሚረዳው እና ከሚሞክረው ስርአት ያፈነገጠ ይለፍ ቃል ( Password ) መጠቀም። ይህም ለምሳሌ አማርኛ ፊደላት ብቻ የያዘ ይለፍ ቃል እጅግ ደህንነቱ የተጠበቀ ነው።
ለ) ሊንኮች ሲላኩልን ቪዲዮ ከሆኑ አውርደው እንዲልኩልን ፅሁፍም ከሆነ ኮፒ በማድረግ እንዲልኩልን በማድረግ እና ከመክፈት በመቆጠብ
ሐ) የፌስቡክ ማጥበቂያ መንገዶችን በመጠቀም
ሐ.1 : ሁለት መግቢያ ማረጋገጫ (2 factor authentication ) መጠቀም ይህም ማለት ፌስቡካችን ውስጥ ሲገባ ወደ ስልካችን የሚላክ ቁጥርን በማስገባት በሁለት አንድ በይለፍ ቃል ሁለተኛ በሚላክልን ቁጥር የማስገባት ሂደት ማረጋገጥ
ሐ.2 : በጣም ደህንነቱ የተጠበቀውን Authentication Factor ወይንም የጎግል የኮድ ማምረቻ ምርት Google Authenticator መተግበሪያ (application) በማውረድ ኮድ እንዲሰጠን ማድረግ ይህ በጣም ደህንነቱ የተጠበቀ ሲሆን ኮዳችንንም በየ 15 ሴኮንዶች ስለሚቀያይር ሰዎች በቀላሉ ማግኘትም ሆነ መገመት አይችሉም።
2) የፌስቡክ ጥቆማ : Facebook Report
በቡድን በመሆን እና በተደጋጋሚ የፌስቡክ ብቻም ሳይሆን የተለያዩ ትስስር ገፆችን መዝጋት ብሎም የእገዳ ገደብ ውስጥ እንዲገቡ ማድረግ የተለመደ ነው። በቡድን መሆን ያስፈለገበት ምክኒያት የጥቆማው ምክኒያት የተሳሳተ እና ብዙ ከሆንን እውነት ይሆናል ከሚል የኢትዮጲያውያን አስተሳሰብ ወደ ቴክኖሎጂው የተቀዳ አመለካከት ነው። ሆኖም ይህ ቴክኖሎጂውን አለአግባብ መጠቀም የሚፈጥረው ተፅእኖ የአካውንቱ ባለቤት አንዳንድ ሂደቶችን አለማወቁን ተከትሎ ነው።
ፌስቡክ በመጀመሪያ የተሳሳቱ ፅሁፎችን ወይንም ልጥፎችን እንዴት ይረዳል?
አንድ ግለሰብ በገፁ ላይ የፌስቡክ ማህበረሰብ መመሪያ (Facebook Community Guidelines ) የሚጣረስ ነገር ሲለጥፍ በቀጥታ እንዲለዩ የተለያየ መረጃ ( training datasets) ተሰጥቷቸው በሰለጠኑ ሰውሰራሽ አስተውህሎቶች (Artificial Intelligence ) ገና እንደተለጠፈ እንዲወርድ ይደረጋል። ይህንን ግን ማለፍ ይችላል ምክኒያቱ ደግሞ ከተሰጣቸው እውቀት ውጪ የሆነ ቃላትን ሆነ የምስል ቅንብር በመጠቀም
ለምሳሌ "ይዘየር" የሚለው ቃል የተለመደ የአማርኛ መዝገበ ቃላት ባለመሆኑ ፅሁፋችን ውስጥ የሚፈጥረው ጥሰት የለም ነገር ግን በሃገራችን ይህ ቃል ከግለሰቦች ፎቶ ጋር ከተያያዘ የሚጥስ ትርጉም መልእክትን ይፈጥራል።
ታድያ ሰዎች በተደጋጋሚ ጥቆማ በሚሰጡበት ወቅት የፌስቡክ ሰውሰራሽ አስተውህሎት ደጋግሞ ያየዋል ነገሩ ያልጣመው ከሆነ ለሰዎች በመላክ እነዛ ሰዎች እንዲገመግሙተሰ ይደረጋል።
ፌስቡክ እንዴት አማርኛ ለመደ?
ይህንን ስራ በመስራት ሂደት ውስጥ የሚገርመው ትልቁ ነገር የፌስቡክ አማርኛ ቃላቶችን መረዳት ነው። ይህ ችሎታ የመጣው በሁለት አይነት መንገድ ነው።
መንገድ - አንድ
የሰው ሰራሽ አስተውህሎት AI ቋንቋውን ወደ እንግሊዘኛ በመቀየር እና ትርጓሜ በመስጠት የፅሁፉን ይዘት ማጣራት ሲሆን ይህም ማህበረሰብን ያስቀይማሉ ተብለው የተሰጡትን ቃላቶች ጋር በማመሳከር ቃላቶቹን በተጠቀሙ ግለሰቦች ላይ ወዲያው እርምጃ እንዲወስድ ያግዘዋል።
መንገድ - ሁለት
ይሄኛው ደግሞ ፌስቡክ በየሃገሩ የሃገሩን ዜጎች ወደ ስራ በማስገባት (ኢትዮጲያኖችን ለኢትዮጲያውያን) በሚለጠፉ ፅሁፎች ዙሪያ የራሳቸውን ውሳኔ እንዲሰጡ ማድረግ ነው። ይህ ማለት አንድ ግለሰብ AI ን ሸውዶ የለጠፈው ፅሁፍ ሰዎች በተደጋጋሚ report ሲያቀርቡ ፅሁፉ የሚላከው ይህንን ቋንቋ ወደሚረዱ ሰራተኛ ክፍሎች ሲሆን እነሱም ከመረመሩ በውሃላ ተገቢውን ምላሽ ይሰጣሉ። በዚህ አይነቱ አካሄድ "ይዘየር" የሚለው ቃል ትርጉሙ በቀላሉ የሚታወቅ እና በቀጣይ AI ሮቦቱ በቀጥታ ፅሁፉን እንዲያወርደው የሚደረገው።
ታድያ ከአውዱ የወጣ በተሳሳተ ጥቆማ የጠፉብንን ፅሁፎች ፣ ፎቶዎች ብሎም የአካውንት እገዳን መልሰን ለፌስቡክ በመጠቆም ማስመለስ ይቻላል ታድያ የፌስቡክ ጥቆማ ብዛት ትክክለኛ ከሆነ አንድ በቂ ነው ካልሆነ ግን መብዛቱ ጥቅም የለውም።
መንገድ - አንድ
ፌስቡክ ይህ ፅሁፍ በዚ ምክኒያት ወርዷል ብሎ መልእክት ሲልክልን መልእክቱን በመክፈት የተሳሳተ ጥቆማ እንደሆነ እና በዚህ በዚህ ምክኒያት ብሎ በማስረዳት የሚመለስበት ሂደት አለ። ይህ የምንፅፈው መልእክት ቀጥታ ሰራተኞች ጋር እንዲታይ ስለሆነ የሚደረገው በሰአታት ውስጥ ትክክለኛ ምላሽ እንድናገኝ የሚያደርገን ነው።
መልካም ሳምንት https://t.me/+5Frg8L1fvwxkMDk0

14/03/2024

Head over to GetIt Addis now and explore the endless possibilities:
አሁን ወደ GetIt Addis ይሂዱ እና ማለቂያ የሌላቸውን አማራጮች ይሸምቱ፡-

Address

Addis Ababa

Telephone

+251713080954

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when GetIt Addis posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share