12/02/2026
ማስታወቂያ ለአርባ ምንጭ ከተማና አካባቢዋ ነዋሪዎች
በአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ማስተማሪያ እና ኮምፕርሄንሲቭ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ከየካቲት 9- 13 /2018 ዓ.ም ከአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ጥቁር አንበሳ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል የሚመጡ ሰብ-ስፔሻሊስት ሐኪሞች በሆስፒታሉ ካሉ የዘርፉ ሐኪሞች ጋር በጋራ በመሆን የሠገራ መውጫ አካባቢ ፊስቱላ (perianal fistula) ፣ ኪንታሮት (Hemorrhoid)፣ የትልቁ አንጀት ካንሰር፣ የእንቅርትና የጡት እባጮችና የካንሰር ቀዶ ጥገና አገልግሎት ይሰጣሉ።
ስለሆነም ከላይ የተጠቀሱ የጤና እክሎች ያለባችሁ ግለሰቦች የፊታችን ዓርብ የካቲት 6 /2018 ዓ.ም ለሕክምናው ያግዝ ዘንድ የቅድመ ምርመራና ልየታ ሥራ የሚካሔድ በመሆኑ በሆስፒታሉ ተገኝታችሁ አገልግሎቱን እንድታገኙ በአክብሮት እናሳስባለን።
የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ማስተማሪያ እና ኮምፕርሄንሲቭ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል