15/03/2024
ኢትዮጵያ እና ግብፅ
ናፖሊዮን ግብፅን ከወረረበት እ.ኤ.አ ከ1798 አንስቶ አገሪቱ ለምዕራባዊያን ቁልፍ የንግድና የስትራቴጂ በር ሆና ብትቆይም፤ ኢትዮጵያም ከግብፅ ያልተናነሰ ጠቀሜታ ያበረከተችባቸው ጊዜያት እንደነበሩ ሊዘነጋ አይገባም። ለዚህ ከ1950ቹ መባቻ እስከ 1960 ቹ አጋማሽ ያሉት ጊዜያት ዋቢ ይሆናሉ። ኢትዮጵያ ከአሜሪካ አስተዳድሮች ጋር በፈጠረችው ግብብ አስመራ የሚገኘው የቃኘው የሬዲዮ መገናኛ ጣቢያ የቀይ ባህር ቀጠናን እና የመካከለኛው ምስራቅን የመቆጣጠሪያ ዋነኛውም ነጥብ ሆኖ አገልግሏል። ኢትዮጵያም በተባበሩት መንግስታት ጥላ ስር በኮሪያና በኮንጎ የሰላም ማስከበር ዘመቻዎች ከአሜሪካ መራሹ የምዕራብ ጥምረት ጎን መሰለፏ ተሰሚነቷን በእጅጉ አጉልቶት ቆይቷል ። ይህ መቀየር እስከጀመረበት እስከ 1960ቹ መጀመሪያ ድረስም ኢትዮጵያ የወታደራዊ ፣ የስትራቴጂክ ፣ የሳይንስና የትምህርት ልማት ድጋፎችን ከአሜሪካና ከምዕራባዊያን ስታገኝ ቆይታለች። ግብፆቹ የኃይል አሰላለፋቸውን ወደ ምዕራቡ ጎራ ሲቀይሩ ግን የተሻለ ምርጫ ሆነው ቀረቡ። በአንፃሩ ኢትዮጵያ ራሷን ከሶሻሊስት ጎራ ውስጥ አገኘች ፤ የጂኦስትራቴጂ ፋይዳዋም ተቀዛቀዘ። የዚህና የመጪው ትውልድ እሳቤ ይህንን መቀልበስ በሚቻልበት መንገድ ላይ እና የአገሪቱን ተቀባይነት እና ተሰሚነት ከማጉላቱ ላይ ሊሆን ይገባል።
ኢትዮጵያ እና ጎረቤቶቿ
በበለጠ በላቸው ይሁን
ገፅ 209